ሀ/ በአጥቢያችን የሚገኙ ምዕመናን ብዙዎቹ ሊሰሩና የተሻለ ገቢ በማግኘት ኑሮአቸውን ሊያሻሽሉ ሲችሉ ፤ እንጨትና ቅጠል በመሸጥ የሚያገኙት ገቢ ፤ ለዕለት ጉርስና ለዓመት ልብስ የማይሸፍን ስለሆነ ፤ በዕድሜ የገፉ ወላጆቻቸውን ለመጦር አቅማቸው ባለመቻሉ ለልመና ተደርገዋል።
ለ/ ልጆቻቸውም የሚለብሱትና የሚመገቡት በቂ መተዳደሪያ ከመቸገራቸውም በላይ ፤ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱት መማር ሲገባቸው ፤ በጎዳና ችግር ተጋልጠው ይገኛሉ።
ሐ/ ሠርተው ኑሮአቸውን ለማሽሽል አውሙ ያላቸውንና የመቋቋሚያ ገንዘብ የተቸገሩትን ፤ ችግኝ በማፍለት፣ ወተት አሰባስቦ ከተማ በመሸጥ፣ በእንጨት የሚሰሩ የእጅ ሥራ ውጤቶችን በመሸጥ፣ ጥጥ በመፍተልና በሽመና ሥራ፣ እንጀራ ጋግሮ በመሸጥና በሌሎችም ሥራዎች ተሰማርተው ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ በማድረግ ፤ የቤተሰቦቻቸውን ችግር ለማቃለል ይቻላል።
መ/ የበጎ አድራጎት ክፍሉም በ1999 ዓ.ም. ለማቋቋሚያ የሚሆን ለአንድ ሰው እስከ 10 ሺህ ብር ከ3 ሰው እስከ 30 ሺህ ብር በዕርዳታ ካገኘ ፤ በገንዘቡ ሥራ ሠርተው ቀስ በቀስ እንዲከፍሉና በተመለሰው ገንዘብ ሌሎችም በተመሳሳይ ሁኔታ ፤ በተከታታይና በተመሳሳይ መርሐ ግብር እንዲረሱበት የማድረግ ፤
ሠ/ ወጣቶችንም በተመለከተ በተመሳሳይ መልኩ በአቅም ማነስ ትምህርታቸውን ያቋረጡ በቀን ወይም በማታ እንዲቀጥሉ ፤ ትምህርታቸውን ጨርሰው ለተቀመጡ ተመሪዎች ፤ የልብስ ስፌት፣ የኮምፒዩተርና የመሳሰሉትን ሙያዎች በማሰልጠን የስራ እድል እንዲያገኙና የመስራት ችሎታው እያላቸው የገንዘብ አቅም አጥተው በሙያቸው ለመጠቀም ያልቻሉ ወጣቶች እንዲቋቋሙ የማድረግ እቅድ አለው። ለዚህም ለሦስት ተማሪዎች ለሙያ ሥልጠና ለአንድ ተማሪ 5 ሺህ ብር ለሦስት ተማሪ 15 ሺህ ብር ያስፈልጋል።
ከዚህ በላይ በፊደል ተራ “መ” እና “ሠ” የታቀዱትን ተግባራዊ ለማድረግ እስካሁን በመርዳት ላይ ለሚገኙ ወዳጆቻችን ከዘገባችን ጋር ጥያቄያችንን ብናቀርብም ምላሽ የሰጡ ባለመገኘታቸው ፤ እስካሁን የዕርዳ ሥራው ሊከናወን አልቻለም፡፡